እሑድ 19 ኤፕሪል 2026
05:14:37 ከሰዓት UTC+3 - Addis Ababa
ምናሌ ክፈት
የሀገር ውስጥ
ዓለም አቀፍ
ዲያስፖራ
እሑድ 19 ኤፕሪል 2026
05:14:37 ከሰዓት UTC+3 - Addis Ababa
ወቅታዊ ጽሁፎች
ፖለቲካና ዲፕሎማሲ
ማህበራዊ
ባህልና ኪነ-ጥበባት
ምርጫ 2018
ሳይንስ እና ቴክኖሎጂ
ኢኮኖሚ
ስፖርት
ሕግና ፍትሕ
የአርታዒዎች ምርጫ
ሳይንስ እና ቴክኖሎጂ
ማይክሮሶፍት የሳይበር ደህንነት ማሻሻያ ይፋ አደረገ
በ
ብርሃኑ ተሰማ
•
•
1 ደቂቃ ንባብ
•
AI
በኢትዮጵያ የመንግሥትም ሆነ የግል ተቋማት በተለይም ባንኮችና የፋይናንስ ተቋማት ከነዚህ ወቅታዊ የሳይበር ጥቃቶች መረጃዎቻቸውን ለመጠበቅ፤የዊንዶውስ፣የሼር ፖይንትናና ኦፊት ሶፍትዌሮቻቸውን በአስቸኳይ እንዲያዘምኑ አስተዳደሩ አሳስቧል።
ማይክሮሶፍት ኩባንያ የሚያዝያ 2026 ወርሃዊ የደህንነት ማሻሻያውን ይፋ አድርጓል፡፡
የኢትዮጵያ
የመንግ
ሥትና የግል ተቋማት በተለይም ባንኮችና የፋይናንስ ተቋማት ማሻሻያውን እንዲጠቀሙበት ተጠይቀዋል፡፡
ይኸው ፓትች ቱስዴይ(Patch Tuesday)ተብሎ የተሰየመው ማሻሻያ
167 የሳይበር ደህንነት ክፍተቶችን ዘግቷል።
ከነዚህም ውስጥ ሁለት አስቀድመው ያልታወቁ (Zero-day) ክፍተቶች የሚገኙበት ሲሆን፣ አንደኛው በአሁኑ ወቅት በሳይበር ጥቃት አድራሾች በተግባር ጥቅም ላይ እየዋለ ያለ አደገኛ ክፍተት እንደሆነም ተገልጿል።
ማሻሻያው ስምንት እጅግ አደገኛ (critical) ክፍተቶችን ያካተተ ሲሆን፣ አብዛኛዎቹ ጥቃት አድራሾች በርቀት ሆነው የድርጅት ኮምፒ
ዩተሮችን እንዲያዙ ወይም አደገኛ ትዕዛዞችን እንዲያስኬዱ (remote code execution)ያስችላሉ።
በተለይም በ “SharePoint” ላይ የማታለል ጥቃት (spoofing) ለማድረስ የሚያስችለው ክፍተት (CVE-2026-32201) በጥቃት አድራሾች ጥቅም ላይ መዋሉን የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር መረጃ ያስረዳል፡፡
በተጨማሪም በ “Microsoft Defender” ላይ ያልተገባ የቁጥጥር ደረጃ (privileg
በኢትዮጵያ
e escalation) ለማግኘት የሚያስችለው ክፍተትም በዚሁ ማሻሻያ ተዘግቷል።
በሌላ በኩል የተለያዩ የማይክሮሶፍት ኦፊስ (Word, Excel, PowerPoint) ክፍተቶችም የተጠገኑ ሲሆን፤ አንዳንዶቹ አደገኛ ሰነዶችን (malicious documents) በመክፈት ወይም የፋይሉን ቅድመ እይታ (preview pane) በመመልከት ብቻ ለጥቃት ሊያጋልጡ የሚችሉ ነበሩ።
በኢትዮጵያ የመንግ
ሥትም ሆነ የግል ተቋማት በተለይም ባንኮችና የፋይናንስ ተቋማት ከነዚህ ወቅታዊ የሳይበር ጥቃቶች መረጃዎቻቸውን ለመጠበቅ፤የዊንዶውስ፣የሼር ፖይንትናና ኦፊት ሶፍትዌሮቻቸውን በአስቸኳይ እንዲያዘምኑ አስተዳደሩ አሳስቧል።
የሳይበር ጥቃት
ኢንፎርሜሸን ቴክኖሎጂ
ሳይንስና ቴክኖሎጂ
0
አወድ
0
አስቀምጥ
አስቀምጥ
አጋራ
አጋራ
0 አስተያየቶች
አስተያየት ይላኩ
ገና አስተያየት የለም። የመጀመሪያው አስተያየት ሰጪ ይሁኑ!
0 አስተያየቶች
ገና አስተያየት የለም። የመጀመሪያው አስተያየት ሰጪ ይሁኑ!