እሑድ 19 ኤፕሪል 2026
05:11:28 ከሰዓት UTC+3 - Addis Ababa
ምናሌ ክፈት
የሀገር ውስጥ
ዓለም አቀፍ
ዲያስፖራ
እሑድ 19 ኤፕሪል 2026
05:11:28 ከሰዓት UTC+3 - Addis Ababa
ወቅታዊ ጽሁፎች
ፖለቲካና ዲፕሎማሲ
ማህበራዊ
ባህልና ኪነ-ጥበባት
ምርጫ 2018
ሳይንስ እና ቴክኖሎጂ
ኢኮኖሚ
ስፖርት
ሕግና ፍትሕ
የአርታዒዎች ምርጫ
ስፖርት
ኢትዮጵያ ዓለም አቀፍ የስፖርት ጋዜጠኞች ማህበር ጉባዔን ታስተናግዳለች
በ
ብርሃኑ ተሰማ
•
•
2 ደቂቃ ንባብ
•
AI
ኢትዮጵያ የዓለም አቀፍ በተለይም የአፍሪካ ዲፕሎማሲ መቀመጫ እንደሆነች በየዓመቱ የአፍሪካ ኅብረት መሪዎች ጉባዔን ጨምሮ በርካታ ስብሰባዎችን ታስተናግዳለች፡፡
በተለይም ርዕሰ ከተማ አዲስ አበባ ወትሮም የዓለም አራተኛ የዲፕሎማሲ መዲናዋ የምታስተናግዳቸው እንግዶች ቁጥር ጨምሯል፡፡
በዚያው ልክ የምታስተናግዳቸው ዓለም አቀፍና አህጉራዊ ስብሰባዎች በዚያው ልክ እየተበራከቱ ሄደዋል፤ባለፈው ዓመት ብቻ 150ስብሰባዎች መስተናገዳቸው ሳይረሳ፡፡
አሁን ደግሞ ተራው
የዓለም አቀፍ የስፖርት ጋዜጠኞች ማህበር (AIPS)ሆኗል፡፡
ማህበሩ
ኢትዮጵያ 89ኛውን ጉባዔውን በሚቀጥለው ዓመት እንድታስተናግድ በመምረጡ፡፡
ኢትዮጵያ ጉባዔውን እንድታስተናገድ ወሳኝ ሚና የተጫወተው የኢትዮጵያ ስፖርት ጋዜጠኞች ማህበር መሆኑም ተገልጿል፡፡
የባህልና ስፖርት ሚኒስቴር ዛሬ ባወጣው መግለጫ እንዳመለከተው
መንግሥት ለስፖርት ዘርፍ በሰጠው ልዩ ትኩረት እና እየገነባ ባለው መሠረተ ልማት ስፖርታዊ ሁነቶችና ኮንፈረንሶች ወደ ኢትዮጵያ እያመጣ መሆኑን አመልክቷል።
በሉዛን፤ ስዊዘርላንድ በተካሄደው 88ኛው ዓለም አቀፍ የስፖርት ጋዜጠኞች ማህበር (AIPS) ጉባዔ ላይ ኢትዮጵያ ቀጣዩን ጉባዔ በይፋ እንድታስተናግድ ተመርጣለች።
ይህ ታላቅ ስኬት ለኢትዮጵያ ብሔራዊ ኩራት ከመሆኑም በላይ፣ ለኢትዮጵያ ተጨማሪ ዕድልንም ይዞ የሚመጣ መሆኑን በማመላከት።
ይህ በኢትዮጵያ ታሪክ የመጀመሪያ የሚሆነው ጉባዔ፣ በኢትዮጵያ ስፖርት ጋዜጠኞች ማህበር ባደረገው ስልታዊ ጥረትና መንግሥት በሰጠው ድጋፍ የተገኘ ውጤት መሆኑንም ሚኒስቴሩ ገልጿል።
ኢትዮጵያ ይህን ዓለም አቀፍ ጉባዔ ለማስተናገድ መመረጧ የአገሪቷን የዲፕሎማሲያዊ ብቃትና የሚዲያ ማዕከልነት በዓለም አቀፍ መድረክ ዳግም የሚያረጋግጥ ነው ብሏል።
በተለይም መንግሥት በየደረጃው ዓለም አቀፍ ደረጃቸውን የጠበቁ ስታዲየሞችንና ሁለንተናዊ የስፖርት መሠረተ ልማቶችን ለመገንባት እያከናወነ ያለውን ተግባርና ለዘርፉ የሰጠውን ትኩረት ለዓለም ማህበረሰብ ለማሳየት ዕድል እንደሚፈጥርም ተገልጿል።
የዓለም ስፖርት ጋዜጠኞች በአዲስ አበባ መስተናገዳቸው፥ በስፖርቱ ዘርፍ የተመዘገቡ ስኬቶችን ለማስተዋወቅ፣ የኢትዮጵያን የቱሪዝም ሀብት የበለጠ ለመግለጥ እንዲሁም ለእገር ውስጥ ባለሙያዎች የልምድ ልውውጥ ለመፍጠር ከፍተኛ ፋይዳ ይኖረዋል።
ይህም መንግሥት ስፖርቱን የሰላምና የልማት ምሰሶ ለማድረግ ለሚያደርገው ጥረት ተጨማሪ አቅምና ዓለም አቀፍ ዕውቅና እንደሚሰጥ ሚኒስቴሩ አስታውቋል።
ስፖርት
ገጽታ ግንባታ
0
አወድ
0
አስቀምጥ
አስቀምጥ
አጋራ
አጋራ
0 አስተያየቶች
አስተያየት ይላኩ
ገና አስተያየት የለም። የመጀመሪያው አስተያየት ሰጪ ይሁኑ!
0 አስተያየቶች
ገና አስተያየት የለም። የመጀመሪያው አስተያየት ሰጪ ይሁኑ!