እሑድ 19 ኤፕሪል 2026
03:41:20 ከሰዓት UTC+3 - Addis Ababa
ፖለቲካና ዲፕሎማሲ

ኢዜማ ኢዮብ መሳፍንትን መሪ አድርጎ መረጠ

1 ደቂቃ ንባብ
ኢዜማ ኢዮብ መሳፍንትን መሪ አድርጎ መረጠ
Eyob Mesafint
የኢትዮጵያ ዜጎች ለማህበራዊ ፍትህ(ኢዜማ)ፓርቲ ኢዮብ መሳፍንትን መሪ አድርጎ መረጠ።

ፓርቲው የአመራር ለውጥ ያደረገው አገሪቱ ለሰባተኛው አገራዊ ምርጫ የሚወዳደሩ ዕጩዎችን ምዝገባ አጠናቅቃ ወደ መራጮች ምዝገባ በተሸጋገረችበት ወቅት ነው።

ፓርቲውም የምርጫ ማኒፌስቶውንም ይፋ አድርጓል።

ኢዮብ የፓርቲውን መሪነት ከብርሃኑ ነጋ(ፕሮፈሰር)ተረክበዋል።

ንጋቱ ወልዴ ደግሞ ፓርቲውን በምክትል መሪነት ተመርጠዋል።
የፓርቲው አመራሮች የአገሪቱን ፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ ሁኔታዎችን የሚያሳይ ፖሊሲ አቅርበዋል።

ፖሊሲው የአገር ግንባታ፣ብሔራዊ ጥቅምን ማስጠበቅና አካታች አስተዳደርን የተሰኙ ምሰሶዎች አሉት።

በምሰሶዎቹ ላይ በመመስረት የአገሪቱን ዕጣ ፈንታ የሚወስን ተቋማዊ መረጋጋትና የኢኮኖሚ ልማት አቅጣጫዎች ተመላክተዋል።

ፓርቲው አገራዊ ምርጫ ለማካሄድ ከሦስት ወራት ያነሰ ጊዜ በቀረበት ሁኔታ ያደረገው መተካካት በአዲስና በተነቃቃ መንፈስ ውድድሩን ለመቀላቀል መዘጋጀቱን አሳይቷል።

አዲሱ አመራር ፓርቲው በአዲስ መልክ በቀየሳቸው ስትራቴጂካዊ አቅጣጫዎች በመመራት ለመራጮች አማራጭ ሐሳቦቹን ለማቅረብ መሰናዳቱን አመላካችም ነው።



Addis Ababa

0 አስተያየቶች

ገና አስተያየት የለም። የመጀመሪያው አስተያየት ሰጪ ይሁኑ!